ዛሬ ደግሞ በአምሃ ሬከርድ የወጣውን የጌታቸው ካሳን ሁለት ግሩም ሙዚቃዎች የያዘ ሌላ 7″ ሸክላ ይዘናል::
A. ብቻዬን ተክዤ
B. በይ ልሰናበትሽ
ድምፃዊና ግጥም ደራሲ – ጌታቸው ካሳ
ሙዚቃዎቹን ያቀናበሩት እና የተጫወቱት – ሶል ኤኮስ ባንድ
ይህ ሸክላ የወጣበት ዘመን – 1962 አ.ም
አሳታሚ – አምሃ ሬከርድስ (አምሃ እሸቴ)
አከፋፋይ – ሃራምቤ ሙዚቃ ቤት
ሶል ኤኮስ ባንድ ሙዚቀኞች
ቤዝ – ፈቃደ አምደመስቀል
ጊታር – አሉላ ዮሃንስ
ድራም – ተስፋዬ መኮንን
ኦርጋን (ኪቦርድ) – ተሾመ ምትኩ
ቴነር ሳክስፎን – ቴዎድሮስ ምትኩ
ትራምፔት -ታምራት ፈረንጅ
እነዚህ ሁለት ሙዚቃዎች ሁዋላ ላይ የኢትዮጲክስ ስብስቦች ላይ ተካተዋል:: ብቻዬን ተክዤ – éthiopiques-8: Swinging Addis 1969-1974 ላይ ታገኙታላችሁ::በይ ልሰናበትሽ ደግሞ – éthiopiques-24: Golden Years of modern Ethiopian music 1969-1975 ላይ ይገኛል::
በነገራችን ላይ “በይ ልሰናበትሽ” የተባለው ሙዚቃ የዘመኑን የቁዘማ ወይም የሃዘን ድባብና ትዝታ ውስጥ የሚከት የዜማ ስልት ( melancholic singing) በደምብ የሚያሳይ ነው:: የዜማው አሳዛኝነት እና የግጥሙ ሃሳብ እንዴት እንደተስማሙ ሳስብ ሁሌም ይደንቀኛል::
ሰናይ ቀን ይሁንላችሁ!!
Leave a comment