ጌታቸው ካሳ – “ብቻዬን ተክዤ” እና “በይ ልሰናበትሽ”

ዛሬ ደግሞ በአምሃ ሬከርድ የወጣውን የጌታቸው ካሳን ሁለት ግሩም ሙዚቃዎች የያዘ ሌላ 7″ ሸክላ ይዘናል::

A. ብቻዬን ተክዤ

B. በይ ልሰናበትሽ

ድምፃዊና ግጥም ደራሲ – ጌታቸው ካሳ

ሙዚቃዎቹን ያቀናበሩት እና የተጫወቱት – ሶል ኤኮስ ባንድ

ይህ ሸክላ የወጣበት ዘመን – 1962 አ.ም

አሳታሚ – አምሃ ሬከርድስ (አምሃ እሸቴ)

አከፋፋይ – ሃራምቤ ሙዚቃ ቤት

ሶል ኤኮስ ባንድ ሙዚቀኞች

ቤዝ – ፈቃደ አምደመስቀል

ጊታር – አሉላ ዮሃንስ

ድራም – ተስፋዬ መኮንን

ኦርጋን (ኪቦርድ) – ተሾመ ምትኩ

ቴነር ሳክስፎን – ቴዎድሮስ ምትኩ

ትራምፔት -ታምራት ፈረንጅ

እነዚህ ሁለት ሙዚቃዎች ሁዋላ ላይ የኢትዮጲክስ ስብስቦች ላይ ተካተዋል:: ብቻዬን ተክዤ – éthiopiques-8: Swinging Addis 1969-1974 ላይ ታገኙታላችሁ::በይ ልሰናበትሽ ደግሞ – éthiopiques-24: Golden Years of modern Ethiopian music 1969-1975 ላይ ይገኛል::

በነገራችን ላይ “በይ ልሰናበትሽ” የተባለው ሙዚቃ የዘመኑን የቁዘማ ወይም የሃዘን ድባብና ትዝታ ውስጥ የሚከት የዜማ ስልት ( melancholic singing) በደምብ የሚያሳይ ነው:: የዜማው አሳዛኝነት እና የግጥሙ ሃሳብ እንዴት እንደተስማሙ ሳስብ ሁሌም ይደንቀኛል::

ሰናይ ቀን ይሁንላችሁ!!

··················

Comments

Leave a comment