“ይበቃኛል” – ግርማ በየነ እና “የግሌ ትዝታ” -ሙላቱ አስታጥቄ

ወጣትነት ማቆሚያ የሌለው እምቅ አቅም የሚሰጠን ድንቅ ነገር ነው:: በዚያ ላይ ደግሞ የታደሉት ወደውስጣቸው የሚያዩበት የተደበቀ ስጦታና ፀጋቸውን የሚያወጡበት የጉብዝና ዘመንም ነው:: በወጣትነት ዘመን ላይ ያለን “በዘመኔ ምን እየሰራሁ ነው?” ብለን ራሳችንን ልንጠይቅ ይገባል:: ዘወትር ወጣትና ባለትኩስ ሃይል ሆኖ መቆየት አይቻልም:: እድሜ ይገፋል ጉልበትና አቅምም ይደክማልና:: ከምክር ስንወጣ ደግሞ ቆየት ወዳለ የሙዚቃ ዳሰሳ እንሄዳለን::በዚህ በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ባለ ሁለት ጥንድ ሙዚቃዎች 7″ ሸክላ በአምሃ እሸቴ አማካኝነት ከወጡ የዘመኑ ሙዚቃዎች 160ኛው ሰንዱቅ ነው:: ፎቶው ላይ የምታዩዋቸው ደግሞ The Timeless Ethiopian music pioneers ሙላቱ አስታጥቄ እና ግርማ በየነ ናቸው:: (በወጣትነት ዘመናቸው)በዚህ ሸክላ ላይ ያሉ ሙዚቃዎች ደግሞ A. ይበቃኛልድምፃዊ – ግርማ በየነግጥምና ዜማ ደራሲ – ባህታ ገብረ ህይወትየሙዚቃ ቅንብር – ግርማ በየነይህ ሙዚቃ ሁዋላ ላይ በፍራንሲስ ፋልሴቶ አማካኝነት ከወጡት የኢትዮጲክስ የሙዚቃ አልበሞች ስብስብ መሃል አንዱ በሆነው ኢትዮጲክስ 8 (‘éthiopiques-8: Swinging Addis) ላይ ተካቶዋል::B. የግሌ ትዝታ (በመሳሪያ የተቀነባበረ ሙዚቃ)ሙዚቃ ድርሰት እና ቅንብር – ሙላቱ አስታጥቄይህኛውም ሙዚቃ ኢትዮጲክስ 4 አልበም ላይ ሙሉ የሙላቱ አስታጥቄን ስራዎች የያዘው éthiopiques-4: Ethio Jazz የተባለው አልበም ላይ በመካተት በድጋሚ ለአድማጭ የበቃ ስራ ነው::ይህ ሸክላ

ዘመኑ ደግሞ በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር በ1961 አ.ም ነው::

··················

Comments

Leave a comment