ይህ ሸክላ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ (commercial የሙዚቃ ቅጂ) የመጀመሪያው ሸክላ ሲሆን የወጣበት ዘመን ደግሞ 1961 ዓ.ም ነው። አሳታሚው አምሃ ሬከርድስ (አምሃ እሸቴ) ሲሆን በዚህ ሬከርድ ሌብል ስር ካሳተማቸው 103 RPM ሸክላዎች የመጀመሪያው (ቁጥር AE 100A & AE 100B) እና ቀዳሚውም ነው።
A. ትማርኪያለሽ
B. ያ ታራ
እነዚህን ሙዚቃዎች ያቀናበራቸው ደግሞ ግርማ በየነ ሲሆን እነዚህ ሁለት ሙዚቃዎች ሗላ ላይ በኢትዮጲክስ የአልበም ስብስቦች ውስጥ 9ኛ በሆነውና ሙሉውን የአለማየሁ እሸቴን ሙዚቃዎች የያዘው አልበም éthiopiques-9: Alèmayèhu Eshèté 1969-1974′ (Buda Musique, France) ላይ ተካተዋል።


Leave a comment